The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

ከክልልና የከተማ አስተዳደሮች ተቆጣጣሪ አካላት ጋር ቋሚ የጋራ የምክክር መድረክ ጉባዔ ተካሄደ

የመንግሥት የግዥና የንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ በክልልና የከተማ አሰተዳደሮች የመንግሥት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ተቆጣጣሪ አካላት መካከል 7ኛው ዙር ቋሚ የጋራ የምክክር መድረክ ጉባዔ ግንቦት 16 ቀን 2009 ዓ.ም. በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር አዳራሽ አካሄደ፡፡
አቶ ጆንሴ ገደፋ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ጊዜያዊ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት በአገራችን የተጀመረውን ፈጣን ልማትና የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ቀጣይነት ለማረጋገጥ፣ በመንግሥት ግዥ አፈጻጸም ውስጥ ሊከሰት የሚችል የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትን በአገር ደረጃ ከምንጩ ለማድረቅ እና በምትኩ ተገልጋይን ማዕከል ያደረገ አሠራርን እና መልካም አሰተዳደርን ለማስፈን፣ በሀገር ደረጃ የተጀመረውን የለውጥ ሰራዊት ግንባታ ከዳር ለማድረስና የህዝብ ክንፍን በመለየት በጋራ ቋሚ መድረክ በመገናኘት ከምንግዜውም በበለጠ ተቀናጅተን መሥራት እንደሚጠበቅብን ገልጸዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ የተለያዩ ሃላፊዎች ጽሁፍ ያቀረቡ ሲሆን እየተሻሻለ የሚገኘውን የመንግሥት ግዥና ንብረት አሰተዳደር አዋጅ ያካተታቸውን ጉዳዮች፣ ያለበትን ደረጃ፣የአዋጅ ማሻሻያ ጥናቱ ዋና ዋና ዓላማዎች፣ በጥናቱ ውጤት መሠረት የቀረቡ ዋና ዋና የማሻሻያ ኃሳቦች እና ማሻሻያውን ማድረግ ያስፈለገባቸው ምክንያቶች በመንግሥት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ የግዥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በዝርዝር ቀርቧል፡፡
በመቀጠልም ስለ 2008 ዓ.ም. የቁልፍ የግዥ አመልካቾች አፈጻጸም ሂደትና የወረዳ ኦዲት ሽፋን በአራቱ ለሙከራ የተመረጡ ክልሎች በመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደርኤጀንሲ የግዥ አስተባባሪና የስልጠና አማካሪ፣ የ2008 ዓ.ም. የቁልፍ የግዥ አመልካቾች አፈጻጸም ሂደትና የ2009 ዓ.ም. የወረዳ የግዥ አፈጻጸም ሂደትና የሽፋን ደረጃ በትግራይ ክልል የግዥና ንብረት የስራ ሂደትና በኦሮሚያ የግዥና ንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ ዳይሬክቶሬት እንዲሁም በፌዴራል መስሪያ ቤቶቸና በልማት ድርጅቶች ያለአገልግሎት ተከማችተው ስለሚገኙ የተለያዩ ንብረቶች የተደረገ የዳሰሳ ጥናትን በሚመለከት በመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር ቀርቧል፡፡
በወይይቱ ላይ ከተሳታፊዎች አሰተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን፣ ለጥያቄዎቹም መልስ ተሰጥል፡፡ለአንድ ቀን በቆየው የምክክር መድረክ ውይይት ላይ የክልል ተቆጣጣሪ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት