The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የ2009 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን በሚመለከት ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለመላው የኤጀንሲው ሀላፊዎች እና ሠራተኞች የ2009 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ ሚያዝያ 17/2009 ዓ.ም በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡   
አቶ ፀጋዬ አበበ የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የውይይቱ ዋና ዓላማ የ2009 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸማችን ምን ይመስላል? በቀሪዎቹስ ሁለት ወራት እንዴት አሟልተን እንጨርሳለን? ከመልካም አስተዳደር፤ ከለውጥ ትግበራ፣ ከተገልጋይ፣ ከፋይናንስ፣ ከውስጥ አሠራር፣ ከመማማርና ዕድገት እይታዎች አንፃር ምን አቀድን? ምን ሰራን? ያጋጠሙ ችግሮችና መፍተሄዎቻቸውስ ምን መሆን አንዳለባቸው ለይተን በማውጣት የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ ማተኮር አለብን በማለት የዕለቱን ውይይት ከፍተዋል፡፡
በመቀጠልም በኤጀንሲው ስር ያሉ የየዳይሬክቶሬቶቹ ዳይሬክተሮች የ2009 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸማቸውን በአራቱ ዕይታዎች ማለትም ከተገልጋይ፣ ከፋይናንስ፣ ከውስጥ አሠራር፣ ከመማማርና ዕድገት እይታዎች አንጻር ዕቅድና አፈፃፀማቸውን በማነጻጸር ገለፃ አድርገዋል፡፡ በተጨማሪም የየዳይሬክቶሬቶቹ ዳይሬክተሮች  ያጋጠማቸውን አንኳር አንኳር የሆኑ ችግሮች፣ ስለተወሰዱ የማስተካከያ አሰራሮችና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ላይ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡ ከተነሱ አበይት ነጥቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ፡-
ኤጀንሲው በቂ ያልሆነ የሰራተኞች የስራ ክፍል (የቢሮ ማነስ) መኖሩ፣
የኤጀንሲው የደሞዝ ደረጃ ከስራው ጋር ተመጣጣኝ ያለመሆን (አነሰተኛ ክፍያ መሆኑ)
ከዚህ ችግር አንፃር ነባር ባለሙያዎችን ይዞ ማቆየት ካለመቻሉም በላይ አዳዲስ ባለሙያዎችን ከውጭ ለመቅጠር (በዝውውር) መሟላት አለመቻሉ ከፍተኛ የኤጀንሲው ችግሮች መሆናቸው ተነስቷል፡፡
በተነሱት ጥያቄዎች ላይ የኤጀንሲው ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ጆንሴ ገደፋ በቂ ማብራሪያ በመስጠት የጋራ ግንዛቤ እንዲወሰድ ተደርጓል፡፡
በመጨረሻም የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ አበበ በቀጣይ ይበልጥ ትኩረት ሊሰጡ የሚገቡ ተግባራት መካከል የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ነጥሎ ማውጣትና መፍትሄዎቻቸው ላይ በማተኮር፣ የስነምግባር እሴቶችን በማጎልበት ሙስናን እና ብልሹ አሰራርን በመታገል የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል በማለት የዕለቱን ውይይት ቋጭተዋል፡፡
ለግማሽ ቀን በቆየው የኤጀንሲው የ2009 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ውይይት ላይ የኤጀንሲው የበላይ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት