The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የተቆጣጣሪነት ሚና ላላቸው የፈዴራል ቷቋማት በግዥ አፈጻጸም ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ

የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የተቆጣጣሪነት ሚና ላላቸው ከስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤትና እና ከፍትህ አካላት ለተዉጣጡ ባለሙያዎች በአጠቃላይ በመንግስት ግዥ አፈጻጸም ዙሪያ ከየካቲት 1 እሰከ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሥልጠና ሰጠ፡፡  
የመንግስት ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ትዕግስት ደበበ ሥልጠናዉን የሰጡ ሲሆን፤  ሰለመንግስት ግዥ ታሪካዊ አመጣጥ፣ ስለመንግስት ግዥ ልዩ ባህሪያት እና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳዎች፣ ስለመንግስት ግዥ ዓላማና መሠረታዊ መርሆዎች ትከከለኛ መጠን፣ጥራት፣ምንጭ፣ዋጋና ጊዜ መሆናቸውን፣ ከአድልዎ ነፃ ሰለሆነ አሠራር፣ግልፅነት፣ ለሕዝብ ተጠያቂነት፣ የሀገር ውስጥ አምራቾችን ሰለማበረታት፣ስለልዩ አሰተያየት፣ ስለመንግሰት ግዥ አጠቃላይ ገፅታ፣ስለግዥ ምንነት፣ ዓይነቶችና ሂደት፣የመንግሰት ግዥ ስለሚመራባቸው ሕጋዊ ሠነዶች፣ በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ላይ ያለው አዋጅና ዋና ዋና ይዘቶች ዘርዘር ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በመንግስት ግዥ አስተዳደር ከፍተኛ የግዥ ሥልጠና እና ሙያዊ ድጋፍ ባለሙያ የሆኑት አቶ ታደሰ ከበደ ደግሞ ስለተፈቀዱ የግዥ ዘዴዎች ስለ ግልጽ ጨረታ፣ውስን ጨረታ፣ሁለት ደረጃ ጨረታ፣የመወዳደሪያ ሃሳብ በመጠየቅ፣በዋጋ ማቅረቢያ፣ከአንድ አቅራቢ ሰለሚፈጸም ግዥ፣የግዥ ዘዴ ስሚወሰንበት ሁኔታ በግዥ ዓይነት መጠን ውስብስብነትና ስለአቅራቢዎች ቁጥር ውስንነት በመንግስት ግዥ አፈጻጸም ዙሪያ ከግዥ ባለሙያዎችና አቅራቢዎች ስለሚጠበቅ ስነ-ምግባር፣በመንግስት ግዥ  ውስጥ ሊኖር ስለሚገባ ስነ-ምግባርና በግዢ ላይ የተሰማሩ ሰራተኞች ከሥራ ኃላፊነታቸው አንጻር የጥቅም ግጭትን በሚመለከት ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡

በመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የግዥ አፈጻጸምና ንብረት ማሰወገድ አቤቱታ ማጣራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ነጋሽ ቦንኬ  በበኩላቸዉ አቅራቢዎች በመንግስት ባለበጀት መ/ቤቶች ላይ የሚያቀርቡት አቤቱታ እና የመንግስት መ/ቤቶች በአቅራቢዎች ላይ የሚያቀርቡት የጥፋተኝነት ሪፖርት አጠቃላይ ገጽታ ሥነ-ሥርዓቱና ሰለሚመራባቸው ህጎች፣ አቅራቢዎች በመንግስት ባለበጀት መ/ቤቶች ላይ የሚያቀርቡት አቤቱታ ዋና ዋናዎቹ ጉዳዮች፣ ምክንያቶችና የአቀራረብ ሥነ-ሥርዓት፣ስለግዥ አፈጻጸምና ንብረት አወጋገድ አቤቱታ አጣሪና ውሳኔ ሰጪ ቦርድ ስለሚያጋጠሙ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው፣የመንግስት መ/ቤቶች በአቅራቢዎች ላይ የሚያቀርቡት የጥፋተኝነት ሪፖርት  ሰለሚቀርብባቸው ና ስለማይቀርብባቸው ሁኔታዎች፣በኤጀንሲው የሚደረግ የጥፋተኝነት ሪፖርት ማጣራት ሂደት፣በአቅራቢዎችና በመንግስት መ/ቤቶች በኩል ሰለ የሚታዪ ግድፈቶች ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡
የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የተቆጣጣሪነት ሚና ላላቸው መ/ቤቶች ባዘጋጀዉ በሥልጠና ላይ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች አሰተያየቶች የተጠየቁ ሲሆን፤ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ ተሰጥaል፡፡

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት