Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

የባለስልጣኑ አመራርና ሰራተኞች የተከሏቸውን ችግኞች ተንከባከቡ።

(ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም)፣ የኢፌዴሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሰራተኞች “በመትከል ማንሰራራት” የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም የተከላቸውን ችግኞች የመንከባከብና ውሀ የማጠጣት አከናውነዋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በእንጥጦ ፓርኩ፣ በሸገር ከተማ አስተዳደር ኩራ ጅራ ክፍለ ከተማ፣ በምስራቅ ጉራጊዋ ቡኢ ከተማ እና በሌሎችም አካባቢዎች ከ30000 በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን በእንጦጦ ፓርክ የተተከሉ ችግኞችን ዛሬ የመንከባከብና የውሃ የማጠጣት ስራ ሰርቷል።

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው ሰራተኞችን ያበረታቱት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት እንደገለጹት ችግኞችን መትከል ስኬታችን አይደለም። ይልቁንም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ስኬት ችግኞቹን ከመትከል በዘለለ ተንከባክቦ ለሚፈለጉት አገልግሎት እዲውሉ ማስቻል መሆኑንና ለዚህም የባለስልጣኑ አመራርና ሰራተኞች የተከሏቸውን ችግኞች መንከባከብ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

ውሃ የማጠጣትና የመንከባከብ መርሃ ግብሩ በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *