አዲስ የተሾሙት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው፡፡

(መጋቢት 21/2018 ዓ.ም) የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አምራሮች አዲስ ለተሾሙት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሚኒልክ ሳሙኤል ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት አከናውነዋል፡፡
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት አዲስ የተሾሙት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሚኒልክ ሳሙኤል ወደ ባለስልጣኑ መቀላቀላቸው እንዳስደሰታቸው ገልጸው በመሥሪያ ቤቱ በሚኖራቸው ቆይታ ስኬታማ የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ክብርት ወ/ሮ መሰረት አያይዘውም ክቡር አቶ ሚኒልክ ሳሙኤል ወደ ባለስልጣኑ መቀላቀላቸው ትልቅ ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርና ለተቋሙ ርዕይ ስኬትም ጉልህ አስተዋጽዖ እንደሚኖረው አመላክተዋል፡፡
ክቡር አቶ ሚኒልክ ሳሙኤል በበኩላቸው ወደ ባለስልጣኑ መቀላቀላቸ እንዳስደሰታቸው ገልጸው ለባለስልጣኑ ርዕይ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንደሚያበረክቱ ገልጸዋል፡፡





0 Comments