Skip to contentSkip to main navigation Skip to footer

ባለስልጣኑ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ አካሄደ።

(ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም)፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅትን በተመለከተ ከሠራተኞቹ ጋር ሰፊ የውይይትና የገምገማ መድረክ አካሂዷል።

የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን ያቀረቡት የባለስልጣኑ የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ገረመው ሲሆኑ ባለፈው በጀት ዓመት ባለስልጣኑ ዘመናዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነትን የተላበሰ የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓት ለመገንባት በርካታ ተግባራትን እንዳከናወነ አብራርተዋል። አቶ ዳንኤል በሪፖርታቸው በተለይም የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት (e-GP) አጠቃቀምን በውጤታማነት መመራት፣ የአቅም ግንባታ ስራን ማጠናከር፣ የህግ ማዕቀፎችን ተፈጻሚነት መከታተልና ማስፈጸም እንዲሁም የሀብት አጠቃቀምን ማሳደግ ላይ ከፍተኛ ስራ መሰራቱን አመላክተዋል። 

በዚህም በበጀት ዓመቱ በሲስተም ግዥ የሚፈጽሙ ተቋማት ቁጥር 367 መድረሱን፣ ለ13,913 ባለሙያዎችና አቅራቢዎች በተለያዩ ዘርፎች ሥልጠና መሰጠቱን፣ የአዋጅ ቁጥር 1333/2016 ማስፈጸሚያ መመሪያዎች ሥራ ላይ መዋላቸውን ተከትሎ 42 የሚደርሱ መደበኛ የጨረታ ሰነዶች እና ሌሎች የአሰራር ስርዓቶች መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል።  

አቶ ዳንኤል አክለውም በ2018 በጀት ዓመት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማት ውስንነት፣ የክህሎት ልዩነትና የኢንተርኔት መቆራረጥ በዋናነት ተግዳሮት የነበሩ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ እነዚህን ተግዳሮቶች በመፍታት የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓትን ሙሉ ትግበራ ማረጋገጥ፣ የመንግስት ንብረት ዲጂታል ምዝገባን ማሻሻልና የመረጃ ጥራትን ማጠናከር ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም ከሰራተኞች የተለያዩ ጥያቂዎች እና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

በእለቱ የማጠቃላያ ንግግር ያደረጉትና የቀጣይ የስራ አቅጣጫ የሰጡት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው ተቋሙ ዘመናዊ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓትን በማጠናከር በ2022 ዓ.ም በአፍሪካ አርአያ ከሆኑ ተቆጣጣሪ ተቋማት አንዱ ለመሆን የሰነቀውን ራዕይ ለማሳካት እያንዳንዱ የሥራ ክፍልና ባለሙያ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንዳለበት አሳስበዋል።

ክብርት ወ/ሮ መሰረት በሰጡት የስራ አቅጣጫ በ2019 በጀት ዓመት የታቀዱትን የዲጂታል ለውጥ ስራዎችን ማፋጠን፣ የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማጠናከር፣ የኢፍሊት ትግበራን ማሳደግ፣ የሥርዓት ትስስርን ማሻሻልና ጠንካራ የቁጥጥርና የኦዲት አቀራረብን መተግበር የመንግስትን ሀብት በአግባቡ ለመጠበቅና ብክነትን ለመቀነስ ወሳኝ መሆናቸውን በመግለጽ ሠራተኛው ለዕቅዱ መሳካት የበኩሉን እንዲወጣ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *