The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

የመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ ከክልል አቻ ተቋማት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከፌዴራል፣ ከክልል እና ከከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ተቆጣጣሪ አካላት ጋር በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ነሐሴ 10 ቀን 2010 ዓ.ም. የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት በሀገራችን እየተመዘገበ

ከሚገኘው ሁለንተናዊ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ጋር በተያያዘ መንግስት ከፍተኛ መጠን ያለው በጀት በየዓመቱ ለመንግስት ግዥ እንደሚመድብ፣ ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው የመንግስት ገንዘብ የተዘረጋውን የመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር የህግ ማዕቀፍን ተከትሎ ስራ ላይ እንዲውልና ውጤታማ እንዲሆን በአዋጅ የተሰጡትን ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት በማድረግ በርካታ ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡በመቀጠልም ዋና ዳይሬክተሯ ይህ የጋራ የውይይት መድረክ በሀገር ደረጃ የተናበበ የግዥና ንብረት አሰተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግና በየደረጃው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራን ተጣጥመውና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከማድረግ አንጸር በመንግስት ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ዘርፍ እንደመሆኑ መጠን በአፈጻጸም ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችንም ሆነ መልካም ተሞክሮዎች የምንላቸውን ፊት ለፊት በግልጽ በማንሳት ጥልቀት ያለው ውይይት በማድረግ የምናገኘውን መልካም ልምዶች በመቀመር የሥራዎቻችን ልምድ የምንቀስምበት ሁሌም ለተሻለና ለላቀ ውጤት በመትጋት በተሰማራበት የስራ መስክ ውጤታማ የሆነ፣ ከኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር የጸዳ፣ አድሎአዊ አሰራርን የሚነቅፍ፣ በሀገርና በህዝብ ተጠቃሚነት የሚረካ አዕምሮ በማበልጸግ በግዥ ዙሪያ የተጋረጡ አሉታዊ አመለካከቶችን በማረም ለሕዘባችን ተጠቃሚነት ሚናችንን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡

አቶ ፀጋዬ አበበ በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የግዥ አሰተባባሪና የሥልጠና አማካሪ የሆኑት የ2009 ዓ.ም. የቁልፍ የግዥ አመላካቾች /KPI/ አፈጻጸም ሂደትና የወረዳ ኦዲት ሽፋን በአራቱ /በትግራይ፣ደቡብ፣ኦሮሚያና አማራ/ለሙከራ በተመረጡ ክልሎች KPI እንዲተገብሩ ሥልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የ2009 ዓ.ም. የቁልፍ የግዥ አመላካቾች /KPI/ አፈጻጸም ሂደትና የወረዳ የግዥ አፈጻጸምን ሂደትና የሸፋን ደረጃ ተሞክሮ እንዲሁም የአማራ ክልል የመንግስት ግዥና ንብረት ማሰወገድ አገልግሎት የ2010 ዓ.ም. አፈጻጸምና የጋጠሙ ተግዳሮቶችን በክልሉ ተወካዮች ቀርበዋል፡፡ በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተለያዩ አሰተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ጥያቄዎችም ተነስተው ለጥያቄዎቹም መልስ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ለአንድ ቀን በቆየው በዚህ የምክክር መድረክ ስብሰባ ላይ 100 የሚሆኑ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ከኢትየጵያ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ከፌዴራልና ከክልሎች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከኢትየጵያ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ከፌዴራል እና ከክልል የከተማ አስተዳደር የመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ተቆጣጣሪ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ነሐሴ 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት መንግስት የተለያዩ የልማት ዕቅዶችን ነድፎ ተግባራዊ ለማድረግ መላውን የአገራችንን ህዝቦች በማሰተባበር ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በርካታ የልማት ሥራዎች ሲያከናውን መቆየቱንና ከዚህም የተነሳ በአገራችን በየዓመቱ ከሌሎች ተመሳሳይ ደረጃ ከሚገኙት የአፍሪካ ታዳጊ አገራት ጋር ሲነጻጸር በተሻለ መልኩ የኢኮኖሚ ዕድገት እየተመዘገበ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
በመቀጠልም ዋና ዳይሬክተሯ ይህ የጋራ የውይይት መድረክ ምክከር እንዲያደርግባቸው የተዘጋጁት አጀንዳዎች እስካሁን በንግዱ ማህበረሰብ በኩል የተነሱ ጉዳዮችን አስመልክቶ መንግስት እየወሰደ ያለው እርምጃ በስራ ላይ ያለውን የመንግስት የግዥ ሥርዓት የሚዳስሱ እና የአፈጸጸም ግንዛቤ የሚያሳድጉ መሆኑ እነደሚታመንና ይህ የውይይት መድረክ የመንግሥትን የግዥ ስርዓት እና አሰራሩን ማንኛውንም ወገን በግልጽ መረዳት እነዲችልና አድሎአዊ አሰራርን በመከላከል የልማታችን ፀር የሆነውን ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመታገል ከፍተኛ አሰተዋፅኦ ያለው ከመሆኑም በላይ ለመንግስት ልዩ ልዩ ግዥዎች የተመደበ የህዝብ ገንዘብ ለታለመለት ዓላማና ግብ እንዲውል ከፍተኛ አሰተወጽኦ ያድርጋል ብለው እንደሚያስቡ ገልጸዋል፡፡፡

አቶ ሃብታሙ መንገሻ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የሕግ አገልግሎት ባለሙያ እየተሻሻለ የሚገኘውን የመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር አዋጅ ያካተታቸውን ዋና ዋና ጉዳዮችና ያለበትን ደረጃ፣ አዋጁን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋና ምክንያት፣ ከጨረታ ሽያጭ ጋር ተያይዞ በድረ-ገጽ መመዝገብን በተመለከተ፣ ስለ ፐርፎርማንስ ግዥ፣ ስለ ላይፍ ታይም ኮስት አናሊስስ፣ የኮመን ዩዝርሰ አይተምን በተመለከተ፣ ስለ ልዩ አሰተያየት፣ ስለገበያ ጥናት ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡ አቶ ተስፋዬ ብርሃኑ የመንግስት ግዥና ንብረት ማሰወገድ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር በ2010 በጀት ዓመት በመንግስት ግዥና ንብረት ማሰወገድ አገልግሎት ስለተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ያጋጠሙ ችግሮችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫን በሚመለከት፣ ስለመድን ዋስትና፣ ቶነርና ጎማን በተመለከተ፣ ስለኬሚካል አወጋገድ ጉዳይ፣ ስለዓለም አቀፍ ግዥ፣ስለጥቅል ግዥ፣የአገር ውስጥ ምርትን በሚመለከት በዝርዝር አሰረድተዋል፡፡በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተለያዩ አሰተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ጥያቄዎችም ተነስተው ለጥያቄዎቹም መልስ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ለአንድ ቀን በቆየው በዚህ የምክክር መድረክ ስብሰባ ላይ 150 የሚሆኑ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡


ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

በኤጀንሲው የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድን በሚመለከት ከመላው ሠራተኞች ጋር ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከመላው የኤጀንሲው ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ጋር የ2011 የበጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ሐምሌ 24 ቀን 2010 ዓ.ም በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ–ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የስብሰባው ዓላማ በኤጀንሲው በ2011 የበጀት ዓመት በርካታ ሥራዎችን ለማከናወን የታቀደ ሲሆን፣ ይህ ዕቅድ በትክክል እንዲከናወን ከመላው የኤጀንሲው ሰራተኞች ጋር በጋራ መወያየት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ አድማሱ ማሞ የለውጥ ትግበራ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኤጀንሲውን የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ ያቀረቡ ሲሆን፣ የ2010 በጀት ዓመት በኤጀንሲው የታቀዱ የግቦች አፈጻጸም፣የቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም፣የዓበይት ተግባራት አፈጻጸም፣በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተሰጡ ግብረ-መልሶች፣ሀገራዊ የሁለተኛውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሰረት በማድረግ የታቀደው የኤጄንሲው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ፣ በኤጀንሲው የተደረጉ የስጋት ዳሰሳ ጥናት ሠነድ የኤጄንሲው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ለ2011 የኤጀንሲው ዕቅድ መነሻ ተደርጎ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡

በመቀጠልም ዳይሬክተሩ በ2011 በጀት ዓመት የታቀዱ ግቦችና ዋና ዋና ተግባራት በተመለከተ የተገልጋዮችና ባለድርሻዎችን ዕርካታ ለማሳደግ፣ ለውስጥና የውጭ ተገልጋዩች በዜጎች ቻርተር በተቀመጠ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ መሰረት አገልግሎት መስጠት፣ የሀብት አጠቃቀምና ውጤታማነት በማጎልበት ለኤጄንሲው የተመደበውን በጀት በፕሮግራም በጀት መርህ መሰረት ውጤታማ በሆነ መንገድ በመጠቀምና ስትራቴጂያዊ ግቦችን ማሳካት፣ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሪፎርም ሥራዎችን ማጠናከር፣ የመንግስት ግዥ አስተዳደር አፈፃፀምን ማሻሻል፣ የመንግስት ንብረት አስተዳደር አፈፃፀምን ማሻሻል፣የመንግስት ግዥ እና ንብረት አሰተዳደርና ኦዲትና ቁጥጥር ማጠናከር፣ የግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አወጋገድ አቤቱታዎች እና የጥፋተኝነት ሪፖርቶች ውሳኔ አሰጣጥ ማሻሻል፣ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን በማካተት ተሣታፊነትና ተጠቃሚነት ማሳደግ፣ የሰው ሀብት አቅምን ማሳደግ፣ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና የስራ አካባቢ ምቹነትን ማሳደግ መሆኑን በዝርዝር አሰረድተዋል፡፡በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ላይ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተዉ በተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ማርታ እና የኤጀንሲው ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ጆንሴ ገደፋ የማጠቃለያ ንግግር አድርገው የጋራ ግንዛቤ እንዲወሰድ ተደርጓል፡፡ለአንድ ቀን በቆየው የዉይይት መድረክ ላይ 110 የሚሆኑ የኤጀንሲዉ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

የፌዴራል መንግሥት የግዥና ንብረት አሰተዳደር ኤጀንሲ ከመላው ሠራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከመላው የኤጀንሲው ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ጋር የ2010 የበጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2011 ዕቅድን በተመለከተ ሐምሌ 24 ቀን 2010 ዓ.ም በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ– ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት ኤጀንሲው በ2010 በጀት ዓመት በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ መሆኑንና በበጀት ዓመቱ የተከናወኑትን አበይት አፈጻጸሞችን ግምገማ አሰመልክተው ምን አቀድን? ምን ፈጸምን? ጥንካሬና ድክመታችንስ ምንድነው? ለ2011 በጀት  ዓመት የታቀደው ዕቅድ ምን ይመስላል? የሚለውን  ሃሳብ በማንሳት የብስሰባውን ዓላማ በማሳወቅ ከመላው የኤጀንሲው ሰራተኞች ጋር በጋራ መወያየት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አቶ አድማሱ ማሞ የለውጥ ትግበራ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኤጀንሲውን የ2010 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ያቀረቡ ሲሆን፣የተገልጋዮችን ቻርተርን በሚመለከት በአዲስ መልክ ተጠንቶና ተከልሶ ታትም ለተገልጋዮች እየተሰራጨ መሆኑን፣የኤጀንሲውን አገልግሎት አሰጣጥን በሚመለከት በተገልጋዮች የአስተያየት መስጫ መዝገቦች እና ሳጥኖችን በመጠቀም 30 ተገልጋዮች አስተያየታቸውን በፅሁፍ የሰጡ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 27ቱ ተገልጋዮች በተሰጣቸው አገልግሎት የረኩ መሆናቸውን ሲገልጹ፣ 3ቱ ተገልጋዮች በተሰጣቸው አገልግሎት ዕርካታ ያላገኙና መስተካከል ያለባቸውን በመጥቀስ አስተያየት መሰጠቱን አስረድተዋል፡፡
ዳይሬክተሩ በመንግሥት ግዥ አፈፃፀም ላይ 2274 የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶችና የክልል መ/ቤቶች የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች  መስልጠናቸውን፣ በመንግሥት ንብረት አስተዳደር ላይ 919 የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶችና የክልል መ/ቤቶች የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች  መሰልጠናቸውን፣ በመንግስት ግዥ ዙሪያ ሙያዊ ድጋፍና የተለያዩ መረጃዎች ለጠየቁ 1997 ተገልጋዮች መሰጠታቸውን፣ በመንግሥት ንብረት አስተዳደር ዙሪያ ከተለያዩ መ/ቤቶች ለቀረቡ 90 ጥያቄዎች  ሙያ ድጋፍ መሰጠቱን፣ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያን በሚመለከት በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዘዴዎች በመጠቀም በመንግስት ግዥና ንብረት አሰተዳደር ዙሪያ በርካታ የሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆናቸውን፣የህትመት ሜዲያን በሚመለከት የኤጀንሲውን የሥራ እንቅስቃሴን የሚያሳይ

Read more...

በህይወት እና በተግባቦት ክህሎት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ

በፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በህይወት እና በተግባቦት ክህሎት ዙሪያ ለኤጀንሲው ባለሙያዎች በመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት የስብሰባ አዳራሽ ሰኔ 18 ቀን 2010 ዓ.ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡ ወ/ሮ ፍሬወይኒ ገ/እግዚአብሄር ከትምህርት ስትራቴጂክ ማዕከል የሥርዓተ-ጾታ ባለሙያ የግንዛቤ ማስጨበጫ  ሥልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ የሥልጠናውም ዓላማ ሰለህይወት እና ተግባቦት ክህሎት ምንነት፣ እነዚህን ክህሎቶች እንዴት ማሳደግ እንደሚቻል እና ውጤቱም ጥሩ የሥራ ከባቢ አየር መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አሰልጣኟ በስነ-ልቦናዊ ክህሎት ውስጥ ራስን ማወቅና ማክበር፣ በራስ መተማመን፣ ልበ-ሙሉነት እና ስለግብ የማስቀመጥ ክህሎት ያስረዱ ሲሆን፣ ራስን ማወቅ ለምን አስፈለገ? ራስን ማወቅ ማለት እንድ ሰው ስለራሱ ያለውን አእምሯዊ፣ አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ ጥንካሬና ድክመት አጠቃላይ ሁኔታ ማወቅ ማለት እንደሆነ፣ ራስን  የማወቅ  አቅም እንዴት  ማሳደግ እንደሚቻል፣ በራስ መተማመን ማለት ምን ማለት ነው? በራስ መተማመንን ለማሳደግ ቁልፍ ነጥቦች፣ ስለ ልበ-ሙሉነትና መገለጫዎቹ፣ እንዴት ማዳበር እንደሚቻልና ስለጥቅሞቹ፣ ግብ ማለት ምን ማት ነው? የግብ አይነቶች እና ስኬታማ ግብ ለመጣል የሚያግዙ ቅድመ ሁኔታዎች ምንድናቸው? የሚለውን በዝርዝር አሰረድተዋል፡፡
በመቀጠልም ተግባቦት ምንድነው? ውጤታማ ተግባቦት እንዴት ማዳበር ይቻላል? ስለሂደቱ፣ ውጤታማ ተግባቦት ለመፍጠር ሰለሚያግዙ ክህሎቶች እና ጥቅሞች፣ሰለመመካከርና መደጋገፍ፣ ግብና ጠቀሜታ፣ ሰለውሳኔ አሰጣጥ ክህሎት ውጤታማነት፣ውሳኔ ለመወሰን ሰለሚያግዙ ሂደቶች እና ስልቶች ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡በተሰጠው ሥልጠናው ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች የተነሱና አስተያየቶችም የተሰጡ ሲሆን ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ለግማሽ ቀን በቆየው ሥልጠና ላይ የኤጀንሲው ባለሙያዎች በንቃት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት