The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

News

ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የበላይ አመራሮች በግዥና ንብረት አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ

የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የበላይ አመራሮች በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ዙሪያ ከመጋቢት 26-28/2011 ዓ.ም በዓዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የመሰብሰቢያ አደራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር አጄንሲ ዋና ዳይሬክተር በሥልጠናው ላይ እንደተናገሩት ግዥ ማለት የመንግስትንና የህዝብን ሀብት ለዜጎች ዕኩል የምናካፍልበትና ዕኩል የመግዛትና የመሸጥ ዕድል፣ ዕኩል የማወዳደር ዕድል ስንሰጥ መሆኑን በሚገባ በመግለፅ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የበላይ አመራሮች የተዘጋጀዉን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በይፋ በመክፈት ስልጠናዉን አስጀምረዋል፡፡
አቶ ጆንሴ ገደፋ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ደግሞ በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዙሪያ የሚታዩ የአቅም ክፍተቶችን ዘላቂነት ባለው መልኩ ከመቅረፍ አንጻር ኤጀንሲው ካቀዳቸው ስትራቴጂክ ጉዳዮች መካከል አንዱ በግዥና ንብረት አስተዳደር ፈጻሚ አካላትን አቅም መገንባት መሆኑን ገልጸዋል፡፡በመቀጠልም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከስራ ባህሪያቸው በመነሳት በተለይም ለዩንቨርሲቲዎች በላይ አመራሩ በመንግስት ግዥ አፈጻጸም ዙሪያ ያለበትን ክፍተት ለመሙላት የሚያስችል ግንዛቤ እንዲኖረው ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እንደተዘጋጀ ገልጸዋል፡፡በኤጀንሲው የሚገኙ አሰልጣኞች ሥልጠናውን ሲሰጡ ስለ ግዥ ዓይነቶች፣ ስለመንግስት ግዥ መርሆዎች፣ስለ ግዥ ዕቅድ ዝግጅትና አስፈላጊነት፣ ስለ ዋጋ ማቅረቢያ፣ ስለጨረታ ግምገማ ሂደቶች እና ስለዋጋ ማስተካከያ፣ በግዥ ፈጸሚ መ/ቤቶች ስለሚካሄዱ የአቤቱታ ማጣራት ሂደት፣ አቤቱታ ስለሚቀርብባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፣ ስለጥፋተኝነት ሪፖርት አቀራረብ፣ስለንብረት አስተዳደር የስራ ክፍል ተግባርና ኃላፊነት ስለመንግስት ንብረት አስተዳደር ተግባራት፣ስለንብረት አወጋገድና ስለማስወገጃው አይነቶች በዝርዝርአስረድተዋል፡፡በዚህ ሶስት ቀናት በቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ላይ ከ220 በላይ ከተለያዩ የአገራችን የዩንቨርሲቲ አመራሮች የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን፣ለተነሱት ጥያቄዎችም በኤጀንሲው አመራሮች እና በአሰልጣኞች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡


በኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለዩኒቨርሲቲዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ

የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለዩኒቨርሲቲዎች ከመጋቢት 23-25 /2011 ዓ.ም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡ ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት የስልጠናው ዋና አላማ ታላላቅ ግዥ ፈጻሚ ዩኒቨርሲቲዎች እና የክልል የግዥ ተቋማት ጋር በቅርበት አብሮ በመስራት የመንግስት ግዥ ግልፅነት የተላበሰ፣ቀልጣፋ፣ወጪ ቆጣቢ፣ የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ተመጣጣኝ ገንዘብ እንዲያስገኝ፣ ከሙስና እና ከብልሹ አሰራር የጸዳ እንዲሆን ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል፡፡በመቀጠል የመንግሰት ግዥ አፈጻጸምና ንብረት ማስወገድና አቤቱታ ማጣራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ነጋሽ ቦንኬ ስለመንግስት ግዥ አጠቃላይ ገጽታ፣ የመንግስት ግዥ ስለሚመራባቸው የህግ ማዕቀፎች፣ ስለመንግስት ግዥ ዓላማና መርሆች፣ በመንግስት ግዥ አፈጻጸም ሊኖር ስለሚገባ ተግባር እና ኃላፊነት፣ የአቤቱታና የጥፋተኝነት ሪፖርት ማጣራት ሂደት አጠቃላይ ገጽታ እና በአፈጻጸም የታዩ የአሰራር ችግሮች አጠቃላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡በመቀጠልም የመንግሰት ግዥና ንብረት ኦዲትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘለቀ ታፈሰ ግዢና ንብረት ኦዲት ሂደትና አጠቃላይ ገፅታዎች፣ ስለግዢና ንብረት ኦዲት ትርጉም፣ ስለግዥና ንብርት ኦዲት አላማዎች፣ ኦዲት ተደርገው ስለተገኙ ዋና ዋና ግኝቶች ላይ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል፡፡በመጫረሻም ወ/ሮ መቅደስ ብርሃኑ  ስለመንግስት ተሽከርካዎች ስምሪትና ነዳጅ አጠቃቀም፣ ስለመንግስት ንብረት አወጋገድ ሂደት ላይ አጠቃላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡ክቡር አቶ ጆንሴ ገደፋ የፌዴራልመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በስልጠናው መዝጊያ ላይ ባደረጉት ንግግር ይህ ስልጠና የታለመለትን አላማ ግብ እንዲመታ ሁሉም የተቋማት አመራሮች ጠንክረው መስራት ይኖርባቸዋል ያሉ ሲሆን ኤጀንሲውም መንግስት የጣላበትን ኃለፊነት በእጅጉ ለመወጣት በቆራጥነት የሚሰራ መሆኑ እና አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡የስልጠናውተሳታፊዎችም በርካታ ሃሳቦችን እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ጥያቄዎች ላይ በአጀንሲው አመራሮች ምላሽ ተሰጥቶ ለሶስተ ቀናት የቆየው ስልጠና ተጠናቋል፡፡

በአቅራቢነት ስለመመዝገብ

በኤጀንሲያችን ድረ-ገጽ ላይ በአቅራቢነት በቀላሉ ለመመዝገብ እንዲችሉ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የአጠቃቀም ማኑዋል (User Guide for Supplier) በቅድሚያ መመልከት እንዳለብዎት አይርሱ፡፡ በመመሪያው መሠረት ምዝገባዎን ያከናውኑ፡፡

ኤጀንሲው በ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ገመገመ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ ከመላው የኤጀንሲው ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ጋር ጥር 15 ቀን 2011 ዓ.ም በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልገሎት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡

ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የስብሰባው ዓላማ በዚህ በ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የታቀዱ ተግባራት፣የተከናወኑ ተግባራት፣ያልተከናወኑ ተግባራት እና በዕቅድ ተይዘው ያልተከናወኑበት ምክንያት ለመወያየትና በቀጣይ መሰረት ለማስቀመጥ መሆኑን ለውይይቱ ታዳሚዎች ገልጸዋል፡፡በመቀጠልም ወ/ሮ አበባ ዓለማየሁ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኤጀንሲውን የ2ዐ11 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ አመት የዕቅድ አፈፃፀምን ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፣ ኤጀንሲው በመጀመሪያው ግማሽ አመት ለማከናወን ያቀደቸውን ማለትም የፈፃሚ ዝግጅትን፣ የተገልጋዮችና ባለድርሻዎችን ዕርካታ ማሳደግ፣የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት መፍታት፣ የሀብት አጠቃቀምና ውጤታማነት ማጎልበት፣ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሪፎርም ሥራዎችን ማጠናከር፣ የመንግሥት ግዥ አስተዳደር አፈፃፀምን ማሻሻል፣ ከመ/ቤቶች የሚቀርቡ ዓመታዊ የግዥ እቅዶች በትክክለኛው የጥራት ደረጃ ተዘጋጅተው መቅረባቸውን በመፈተሽ ለመ/ቤቶች ግብረ መልስ መስጠት በሚሉ ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም የግዥ አፈጻጸም እና ንብረት አወጋገድ አቤቱታዎች እና የጥፋተኝነት ሪፖርቶች ውሳኔ አሰጣጥ ማሻሻል፣ የዘርፈ ብዙ ጉዳዩዮችን በማካተት ተሣታፊነትና ተጠቃሚነትን ማሳደግ፣ የለውጥ ሥራዎችን ውጤታማነት ማሳደግ፣ የሰው ሀብት አቅም ማሳደግ፣ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና የሥራ አካባቢ ምቹነት ማሳደግ እና በአጠቃላይ በግማሽ በጀት ዓመቱ የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፣የክትትልና  ግምገማ አፈፃፀም፣ያጋጠሙ ችግሮች፣ የመፍትሔ እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በሚመለከት ሰፊ ማብራሪያ አድርገዋል፡፡

Read more...

በአቅራቢነት ስለመመዝገብ

በኤጀንሲያችን ድረ-ገጽ ላይ በአቅራቢነት በቀላሉ ለመመዝገብ እንዲችሉ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የአጠቃቀም ማኑዋል (User Guide for Supplier) በቅድሚያ መመልከት እንዳለብዎት አይርሱ፡፡ በመመሪያው መሠረት ምዝገባዎን ያከናውኑ፡፡

More Articles...