The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

9ኛው የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል ቀን ተከበረ


የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ከመንግሥት የግዥና የንብረት ማስወገድ አግልግሎት እና ከመንግስት የልማት ድርጅቶች ባላአደራ ቦርድ ጋር በመተባበር የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል ቀንን ህዳር 26 ቀን 2007 ዓ.ም. በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር  አዳራሽ በድምቀት አከበረ፡፡

በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሀጂ ኢብሳ እንደተናገሩት “በሕገ መንግሥታችን  የደመቀ ኢትዮጵያዊነታችን  ለህዳሴያችን” የበዓሉ  መሪ ቃል መሆኑን ገልጸው ሀገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ የህዝቦቿን ጥቅም የሚያረጋግጥ ህg መንግስታዊ ስርዓት ለመመስረት በህዝቦቿ ፈቃድና ፍላጎት ህገ መንግስት አፅድቃ መንቀሳቀስ ከጀመረች 20 ዓመታት እንደተቆጠረ፣ህገ መንግስታችን የሁሉም ህጎች የበላይ የሆነ የህግና የፖለቲካ ሰነድ እንደሆነ፣አገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ታሪካዊ ክስተቶችን ያስተናገደች አገር እንደሆነች፣የኢትዮጵያ ህዝቦች በታሪካቸው በርካታ ተጋድሎዎችን መፈጸማቸውን፣ከአድዋ የድል ታሪክ ቀጥሎ በአገራችን ትልቅ ትዕንግርት የተሰራው በህገ መንግስቱ መፅደቅና ለዚሁ ምክንያት በሆነው ተጋድሎ መሆኑን በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያ አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም ሕገ መንግስት፥ ብዝሀነት፥ ልማት፥ ዲሞክራሲና ብሄራዊ መግባባት፣የህገ መንግስት፥ እሴቶች፥ ባህሪያትና ዓላማዎች፣የተዛቡ ታሪካዊ ገጽታዎች እንዲስተካከሉ የሚያደርግ፣ለመሰረታዊ ቅራኔዎች መልስ የሚሰጥ ፣የህግ የበላይነትና የልማት ትስስር የሚቀበል ህገ መንግስት፣በህዝቦች መደጋገፍ ላይ የተመሰረተ፣ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ፣ እና ዋስትና ያለው ዲሞክራሲ መገንባት በሚሉ ሃሳቦች ላይ   ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ህዳር 26 ቀን 2007 ዓ.ም. በተከበረው የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር፣ የመንግሥት የግዥና የንብረት ማስወገድ አግልግሎት እና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ባላአደራ ቦርድ  መ/ቤቶች የብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል ቀን ላይ ከ400 በላይ ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡

የፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤ  የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት