The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

በቁልፍ የግዥ አፈፃፀም መለኪያ/(KPI) ዙሪያ ከክልል ተቆጣጣሪ አካላት ጋር አዉደ ጥናት ተካሄደ

የፌዴራል መንግስት የግዥና የንብረት አሥተዳደር ኤጀንሲ ከክልል ተቆጣጣሪ አካላት፣ ከክልል ዕድገት ተኮር ቢሮዎች እና ከተመረጡ   የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች ጋር በቁልፍ ግዥ አፈጻጸም መለኪያ ዙሪያ እንዲሁም በወረዳ የግዥ ኦዲት አፈፃፀምን በሚመለከት ከሐምሌ 2 እስከ 4 ቀን 2011 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ ቶሚ ኢንተርናሽናል ሆቴል አዉደጥናት አካሄደ፡፡አቶ ነቢዩ ኮከብ በመንግስት ግዥና ንብረት አሥተዳደር አጄንሲ የዋና ዳይሬክተር አማካሪ የሆኑት በአዉደ ጥናቱ መክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ እንደተናገሩት የዚህ አዉደ ጥናት ዋና ዓላማ የመንግሥት ግዥና ንብረት አሥተዳደር ኤጀንሲ በቁልፍ ግዥ አፈፃፀም አመልካቾች ትግበራ በተለይ በአራቱ ክልሎች (በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በደቡብ እና በአማራ) ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታት አበረታች ቢሆንም በሰባቱ የተመረጡ የፌደራል መ/ቤቶች እና በሌሎቹ ክልሎች ያለው አፈፃፀም ደካማ ስለሆነ ምክንያቶቹን ነቅሶ በማውጣት በመፍትሔዎቹ ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ፣ ቁልፍ የግዥ አፈፃፀም አመልካቾችን በመተግበር ረገድ የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ክልሎች  ልምዳቸውን ለሌሎች እንዲያካፍሉ ማድረግ እና የክልል ወረዳዎች የግዥ ኦዲት አፈፃፀም የሚገኝበትን ደረጃ በጋራ በመገምገም ለወደፊቱ አቅጣጫ በማስቀመጥ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አቶ ፀጋዬ አበበ በመንግሥት ግዥና ንብረት አሥተዳደር ኤጀንሲ የአለም ባንክ ፕሮጀክት የግዥ አስተባባሪና የስልጠና አማካሪ ስለቁልፍ ግዥ አፈፃፀም መለኪያ አመልካቾች ፅንሰ ሃሳብ ምንነትና አስፈላጊነት፣ ስምምነት በተደረሰባቸዉ የቁልፍ ግዥ አፈፃፀም መለኪያዎች፣የቁልፍ ግዥ አፈፃፀም አመልካቾች ሂደት አጠቃላይ ገጽታ እና የአራቱ ክልሎች ቁልፍ የግዥ አፈፃፀም መለኪያ ተሞክሮዎች እና ተግዳሮቶች እንድሁም የወረዳ ግዥ ኦዲት አፈፃፀምን በሚመለከት ሰፋ ያለ ማብራሪያና ገለፃ አድርገዋል፡፡ከሁሉም ክልል ተቆጣጣሪ አካላት፣ከክልል ዕድገት ተኮር ቢሮዎች እና ከፌዴራል     ቁልፍ የግዥ አፈፃፀም መለኪያን ተግባራዊ እንዲያደርጉ በሙከራ ደረጃ ከተመረጡ ባለበጀት መ/ቤቶች ጋር ለሚደረግ አዉደ ጥናት ላይ የተሳተፉ ተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዉ፤ ለተነሱት ጥያቄዎች በቂ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ለሶስት ቀናት በቆየው የቁልፍ ግዥ አፈፃፀም መለኪያዎች /KEY PROCUREMENT INDICATORS/ ለተካሄደዉ አዉደ ጥናት ዉይይት መድረክ ላይ ከ100 በላይ የክልል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡