The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

ለፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች በግዥ አፈጻጸም እና የንብረት አስተዳደር ዙሪያ የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠና ተሰጠ

በፌዴራል መንግስት የግዥና የንብረት አሥተዳደር ኤጀንሲ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ለፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች በግዥ አፈጻጸም እና የንብረት አሥተዳደር ዙሪያ እንዲሁም ደረጃ ለወጣላቸው ዕቃዎች የተዘጋጀውን ስፔሲፊኬሽን በሚመለከት ሰኔ 24 ቀን 2011ዓ.ም. በገንዘብ ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠና ተሰጠ፡፡አቶ ነቢዩ ኮከብ በመንግስት ግዥና ንብረት አሥተዳደር አጄንሲ የዋና ዳይሬክተር አማካሪ የሆኑት በሥልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት የዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ዋና ዓላማ በመንግሥት ግዥና ንብረት አሥተዳደር ኤጀንሲ እና በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ትብብር ደረጃ የወጣላቸውን በመ/ቤቶች በጋራ የሚፈለጉ ዕቃዎችን ግዥ በመፈጸም ረገድ ልንከተላቸው የሚገቡ አሰራሮችን እና ደረጃ ለወጣላቸው ዕቃዎች የተዘጋጀውን ስፔሲፊኬሽን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ያሉ ችግሮችን እና ክፍተቶችን በመለየት መ/ቤቶች ግዥ በሚፈጽሙበት ጊዜ የተዘጋጀውን ስፔሲፊኬሽን በመጠቀም የኢትዮጵያ የጥራት ደረጃን የሚያሟሉና ደረጃቸውን የጠበቁ ዕቃዎችን በመግዛት በመንግስት ገንዘብ የሚገዙ ዕቃዎች ከወጣባቸው ገንዘብ ጋር ተመጣጠኝ የሆነ ፋይዳ እንዲያገኙ በማድረግረገድ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እነደሆነ ገልጸዋል፡፡በመቀጠልም የዋና ዳይሬክተር አማካሪው ደረጃ  በወጣላቸው ዕቃዎች አተገባበር ዙሪያ ግዥ ፈጻሚ መ/ቤቶች በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ በማድረግ በመንግሥት ግዥ ዘርፍ ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ አፈጸጸም እንዲኖር ማስቻል መሆኑን አብራርተዋል፡፡አቶ ወርቁ በዛብህ በመንግሥት ግዥና ንብረት አሥተዳደር ኤጀንሲ ባለቤት የሌላቸው ንብረቶች ቡድን መሪ ስለግዥ ምንነት፣ ስለግዥ ዓይነቶች ስለመንግስት ግዥ መርሆዎች፣ ስለአጽዳቂ ኮሚቴ ተግባርና ኃላፊነት፣ ስለ አቤቱታ አጣሪና ውሳኔ ሰጪ ቦርድ ተግባርና ኃላፊነት  ስለግዥ ዕቅድ፣ ስለተፈቀዱ የግዥ ዘዴዎች እና ስለ ግልጽ ጨረታ ዝርዝር አፈጻጸም ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡አቶ ይስማው ጅሩ በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ሥልጠና የሰጡ ሲሆን፣ ደረጃ ምንድነው? ደረጃ ለምን ያስፈልጋል? ስለጥራት መሰረታዊ ጽንሰ ሃሳብ፣ ደረጃን መተግበር ስለሚያስገኘው ጥቅም፣ ስለጥራት የተሳሳተ ግንዛቤዎች፣ ደረጃ አውጪዎች በዋናነት ሰለሚኖራቸው ድርሻ እና ስለኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ አመሰራረት በዝርዝር አብራርተዋል፡፡አቶ ይልማ መንግሥቱ በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ የደረጃዎች ዝግጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት የግዥ ትግበራ ስለመጠቀም፣ ስለግዥ ፈጻሚዎቸ ሚና፣ የደረጃ መነሻዎች በአማካሪ ቢጠና ምን ችግር አለው? በመንግሥት ግዥ ማዕቀፍ ውስጥ እንዴት ግዥ ይፈጸማል? ትግበራ  በማን ይረጋገጣል? ትግባራዊነቱ ምን ላይ እነደሆነና ስለ ግዥ ደረጃዎች ዓላማ ስልጠና ሰጥተዋል፡፡በቀረበው ገለጻና ማብራሪያ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ለአንድ ቀን በቆየው አፈጻጸም እና የንብረት አሥተዳደር ዙሪያ እንዲሁም ደረጃ ለወጣላቸው ዕቃዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ ከ100 በላይ የፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
በፌ.መ.ግ.ን.አ.ኤጀንሲ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት