The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለዩኒቨርሲቲዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ

የፌዴራል መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለዩኒቨርሲቲዎች ከመጋቢት 23-25 /2011 ዓ.ም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡ ክብርት ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት የስልጠናው ዋና አላማ ታላላቅ ግዥ ፈጻሚ ዩኒቨርሲቲዎች እና የክልል የግዥ ተቋማት ጋር በቅርበት አብሮ በመስራት የመንግስት ግዥ ግልፅነት የተላበሰ፣ቀልጣፋ፣ወጪ ቆጣቢ፣ የመንግስት ገንዘብ ሊያስገኝ የሚችለውን ተመጣጣኝ ገንዘብ እንዲያስገኝ፣ ከሙስና እና ከብልሹ አሰራር የጸዳ እንዲሆን ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል፡፡በመቀጠል የመንግሰት ግዥ አፈጻጸምና ንብረት ማስወገድና አቤቱታ ማጣራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ነጋሽ ቦንኬ ስለመንግስት ግዥ አጠቃላይ ገጽታ፣ የመንግስት ግዥ ስለሚመራባቸው የህግ ማዕቀፎች፣ ስለመንግስት ግዥ ዓላማና መርሆች፣ በመንግስት ግዥ አፈጻጸም ሊኖር ስለሚገባ ተግባር እና ኃላፊነት፣ የአቤቱታና የጥፋተኝነት ሪፖርት ማጣራት ሂደት አጠቃላይ ገጽታ እና በአፈጻጸም የታዩ የአሰራር ችግሮች አጠቃላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡በመቀጠልም የመንግሰት ግዥና ንብረት ኦዲትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘለቀ ታፈሰ ግዢና ንብረት ኦዲት ሂደትና አጠቃላይ ገፅታዎች፣ ስለግዢና ንብረት ኦዲት ትርጉም፣ ስለግዥና ንብርት ኦዲት አላማዎች፣ ኦዲት ተደርገው ስለተገኙ ዋና ዋና ግኝቶች ላይ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል፡፡በመጫረሻም ወ/ሮ መቅደስ ብርሃኑ  ስለመንግስት ተሽከርካዎች ስምሪትና ነዳጅ አጠቃቀም፣ ስለመንግስት ንብረት አወጋገድ ሂደት ላይ አጠቃላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡ክቡር አቶ ጆንሴ ገደፋ የፌዴራልመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በስልጠናው መዝጊያ ላይ ባደረጉት ንግግር ይህ ስልጠና የታለመለትን አላማ ግብ እንዲመታ ሁሉም የተቋማት አመራሮች ጠንክረው መስራት ይኖርባቸዋል ያሉ ሲሆን ኤጀንሲውም መንግስት የጣላበትን ኃለፊነት በእጅጉ ለመወጣት በቆራጥነት የሚሰራ መሆኑ እና አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡የስልጠናውተሳታፊዎችም በርካታ ሃሳቦችን እና ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ጥያቄዎች ላይ በአጀንሲው አመራሮች ምላሽ ተሰጥቶ ለሶስተ ቀናት የቆየው ስልጠና ተጠናቋል፡፡