The FDRE Public Procurement and Property Authority

በኢፌዲሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን

የ2010 በጀት ዓመት የ6 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን በሚመለከት ውይይት ተካሄደ

የፌዴራል መንግሥት የግዥና የንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ለመላው የኤጀንሲው ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የ2010 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን በተመለከተ ጥር 22 ቀን 2010 ዓ.ም. በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አዳራሽ ውይይት አካሄደ፡፡አቶ ጆንሴ ገደፋ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ተ/ዋና ዳይሬክተር በመክፈቻው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት የውይይቱ ዋና ዓላማ የ2010 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸማችን ምን እንደሚመስልና በቀጣይ የስድስት ወራት በጀት ዓመት ለምንሰራው ስራ አቅጣጫ መያዝ እንዳለብን፣ አዲስ በተዘጋጀው የውጤት ተኮር መመሪያ እና የምደባ አካሄድ እንዲሁም በሙሰና መከላከል ሰትራቴጂክ ዕቅድ ላይ በማተኮር ውይይት እንደሚደረግ በመግለጽ ስብሰባውን ከፍተዋል፡፡

አቶ አድማሱ ማሞ የለውጥ ትግበራ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2010 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን በሚመለከት የለውጥና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም የመደበኛ ሥራዎች የ2010 የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በጥንካሬና በዕጥረት የታየ ሲሆን፣ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዕቅድ አፈፃፀምን በማጠቃለል፣ በከይዘን፣ በለውጥና መልካም አስተዳደር ዙሪያ ባጋጠሙ ችግሮችና በተወሰዱ የማስተካከያ አሰራሮች ላይ በሰፊው ውይይት አድርገዋል፡፡አቶ መስፍን መኮንን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በተሻሻለው የውጤት ተኮር ዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራና የአፈጻጸም ምዘና መመሪያ መነሻዎች፣ ዓላማዎች፣ የሰራተኛ የውጤት ተኮር ዕቅድ ዝግጅት፣ የአፈፃፀም ስምምነት፣  ክትትልና  ግምገማ፣ የአፈጻጸም ምዘና፣ የውጤት ተኮር ሥራ አፈጻጸም ምዘና ደረጃ አሰጣጥ፣ድህረ ምዘና ተግባራት እና የልዩ ልዩ አካላት ተግባርና ኃላፊነትን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥተዋል፡፡
በመቀጠልም አቶ መስፍን በነጥብ የሥራ  ምዘናና  ደረጃ  አወሳሰን  የድልድል  አፈፃፀም  መመሪያን በሚመለከት ስለድልድል መመሪያው ዓላማ፣ መርሆዎች፣ የሠራተኛ ውድድር/ድልድል አፈጻጸም፣ አዎንታዊ ድጋፍ፣ የሠራተኞች ለድልድል ማሟላት  የሚገባቸው  ቅድመ ሁኔታዎች፣ የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ሂደት እና የመመዘኛ መስፈርቶች ላይ ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል፡፡

ከመ.ግ.ን.አ.ኤ. የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት