የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በስትራይድ ኢትዮጵያ ኤክስፖ 2024 ማጠቃለያ ፕሮግራም የእዉቅና ሽልማት ተበረከተለት፡፡
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስቴር አዘጋጅነት በሳይንስ ሙዚየም በተካሄደዉ ስትራይድ አዋርድ 2024 ኤክስፖ ብቃት የመለያ ምልክታቸው፤ የአመራር ጥበብ ግለ-ተሰጥኦቸው የሆኑት የዚሁ ቀናዒ ተግባር መሪ(ባለቤት) የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሃጂ ኢብሳ በስፍራው በመገኘት ሽልማታቸውን በክብር ተቀብለዋል፡፡
ባለስልጣኑ በኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ትግበራ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ያበረከተዉ አስተዋጽኦ ከፍ ባለና በላቀ ዉጤት ታጅቦ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ የሃገር ሀብት በተገቢው የግብይት ስርዓት እንዲፈጸም በማድረግ ከብክነት በመታደጉ ረገድ ለነበረው አበርክቶ እና ጉልህ ተሳትፎ የተሰጠ እውቅና መሆኑ ተገልጿል፡፡
በማጠቃለያ ስነ-ስርዓቱ ሚኒስቴሮችን ጨምሮ ሌሎች በግሉ ዘርፍ የተሰማሩ ተሳታፊዎች የተካተቱ ሲሆን በቴክኖሎጂው ዘርፍ የጎላ ሚና ለነበራቸው በርካታ ተሳታፊዎች ጭምር እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
በመጨረሻም የሚኒስቴር መ/ቤቱ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ ስትራይድ ኢትዮጵያ ኤክስፖ በየአመቱ የሚከናወን ሲሆን በፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከአሁናዊ ተግባር በተሻለ ተስፋ ሰጭ ውጤት የሚጠበቅበት ስለሚሆን በሁሉም ዘርፍ ታቅዶበት ሊሰራ እንደሚገባ በአጽንኦት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡
0 Comments